የሀማስ ጊዜያዊ መሪ ካሊድ ማሻልን ጨምሮ ሌሎች የቡድኑ የፖለቲካ ቢሮ አመራሮች በኳታር ይኖራሉኳታር በሀገሪቱ የሚኖሩ ከፍተኛ የሀማስ አመራሮችን ለማስወጣት ከአሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄ መቀበሏ ተሰማ፡፡ሀማስ በ2012 በሶርያ የእርስ በእርስ ግጭት መቀስቀሱን ተከትሎ ዋና ቢሮውን ከደማስቆ ወደ ዶሃ አዘዋውሯል፡፡የጥቅምት ሰባቱን ጥቃት ተከትሎ አሜሪካ “ኳታር በተለመደው መንገድ ከቡድኑ ጋር ግንኙነቷን መቀጠል እንደማትችል” ስታስጠነቅቅ ሰንብታለች፡፡ ሀገሪቱ በዶሃ የሚገኘውን የቡድኑን ዋና ቢሮ እንድትዘጋ እና ለሀላፊዎቹ ጥገኝነት ከመስጠት እንድትቆጠብ ጫና ስታደርግ መቆየቷን ሲኤንኤን የአሜሪካ እና ኳታር ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡ዘገባው ሀማስ ታጋቾችን ለመልቀቅ እና የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ የቀረበለትን ተደጋጋሚ ጥያቅ ውድቅ ማድረጉን ተከትሎ፤ መሪዎቹ በማንኛውም የአሜሪካ አጋር ዋና ከተሞች ተቀባይነት ሊያገኙ አይገባም የሚል ሀሳብ በዋሽንግተን በኩል መንጸባረቁን ጠቅሷል፡፡
al-ain
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች