October 16, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ተቋምን ብሎም ሀገርን ለማገልገል በቅድሚያ ጥብቅ በሆነ ሙያዊ ዲስፕሊን መታነፅ ያስፈልጋል – ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ

የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጆችን በአየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ተቀብለው አነጋግረዋል። አዛዡ በዚህ ወቅት ሀገርን ብሎም ተቋምን ለማገልገል በቅድሚያ የሀገር ፍቅር ስሜት ከአላማ ፅናት ጋር መላበስ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የእርስ በእርስ መደጋገፍን እንደባህል መያዝ እንደሚገባ እና ከፋፋይ ከሆኑ ጎጂ አስተሳሰቦችም መራቅ ወሳኝ ነጥብ መሆኑንም ጠቁመዋል። የበረራ አስተናጋጆች ውስጣዊ አንድነታቸውን ይበልጥ በማጎልበት ከብሔርተኝነት ከሃይማኖት አክራሪነት እንዲሁም ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ራሳቸውን ማራቅ እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል።