የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦርድ ሰብሳቢ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰልጣኝ የበረራ አስተናጋጆችን በአየር ኃይል ጠቅላይ መምሪያ ተቀብለው አነጋግረዋል። አዛዡ በዚህ ወቅት ሀገርን ብሎም ተቋምን ለማገልገል በቅድሚያ የሀገር ፍቅር ስሜት ከአላማ ፅናት ጋር መላበስ እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው፤ የእርስ በእርስ መደጋገፍን እንደባህል መያዝ እንደሚገባ እና ከፋፋይ ከሆኑ ጎጂ አስተሳሰቦችም መራቅ ወሳኝ ነጥብ መሆኑንም ጠቁመዋል። የበረራ አስተናጋጆች ውስጣዊ አንድነታቸውን ይበልጥ በማጎልበት ከብሔርተኝነት ከሃይማኖት አክራሪነት እንዲሁም ከፖለቲካዊ ወገንተኝነት ራሳቸውን ማራቅ እንደሚገባቸውም አስገንዝበዋል።
Woreda to World
More Stories
ምሽቱን በአዲስ አበባ የተለያዩ አካባቢዎች የተከሰተው የመሬት ንዝረት ለ18 ሰከንድ ያህል የቆየ ነው – ዶ/ር ኤልያስ ሌዊ
የሁለቱ ምክር ቤቶች የጋራ መክፈቻ ስነ-ስርዓት ነገ ይካሄዳል
አቶ ሽመልስ አብዲሳ የ ‘ሆረ ፊንፊኔ’ ኢሬቻ በዓል በድምቀት እንዲከበር ያደረጉ አካላትን አመሰገኑ