ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።የፌዴራል የሥነ-ምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ከኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የብሔራዊ የሙስና ወንጀል መረጃ ጥቆማ የዲጂታል አሰራር ሥርዓት መተግበሪያ ማስጀመሪያ መርሐግብር በዛሬው ዕለት ተከናውኗል።ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በመርሐ ግብሩ ላይ እንዳሉት÷ ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው።በተለያዩ መንገዶች የሚከናወነው የጥቆማ አሰጣጥ ሁሉንም ዜጋ የሚያሳትፍና በተለያዩ የሙስና ወንጀል ደረጃዎች ተከፋፍሎ የማጣሪያ አካሔዶችን እንደሚያልፍ ተጠቁሟል።መተግበሪያው ከእጅ ስልክ ጀምሮ በመስሪያ ቤቶች በሚኖሩ ኮምፒውተሮች በመጠቀም የሚከናወን ሲሆን የመከታተያና የማጣሪያ አካሔድ እንደሚኖርም ነው የተገለጸው።መተግበሪያው ጥቆማዎችን በአማርኛ፣ አፋን ኦሮሞ፣ ትግርኛ፣ ሶማሊኛና እንግሊዘኛ ቋንቋዎች መስጠት የሚያስችል እንደሆነም ተመላክቷል።በኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት የተዘጋጀው የዲጂታል አሰራር አራት ወራት መፍጀቱ የተገለጸ ሲሆን ዜጎችን ያሳተፈ የጸረ-ሙስና ስራን ለማከናወን ያስችላል ነው የተባለው።
FBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።
ያለፉት ሁለት ወራት የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲው በስኬታማ አፈፃፀም ላይ መሆኑን አሳይተዋል – ጠ/ሚ ዐቢይ(ዶ/ር)