በሊባኖስ በመሸገው ሂዝቦላህ ላይ የሚወሰደው ሁለንተናዊ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ገልጿል፡፡በዛሬው ዕለትም በቤሩት በተመረጡ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ላይ የተሳካ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ጦር ባወጣው መግለጫ አመላክቷል፡፡በዚህም የሂዝቦላህ ደህንነት ሃላፊና የማዕከላዊ ም/ቤቱ ወሳኝ አባል ነቢል ኳዑክ መገደሉን ነው ያስታወቀው፡፡ በአንጻሩ በከፍተኛ አመራሩ መገደል ዙሪያ ሂዝቦላህ ያለው ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል፡፡እስራኤል በሂዝቦላህ ላይ እየወሰደች ባለው ወታደራዊ እርምጃ የቡድኑን መሪ ሀሰን ነስራላህን ባሳለፍነው አርብ መግደሏ ይታወሳል፡፡
እስራኤል በሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ላይ ጥቃት ተጨማሪ የሂዝቦላህ ከፍተኛ አመራር መግደሏን አስታውቃለች፡፡

More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች