በሊባኖስ በመሸገው ሂዝቦላህ ላይ የሚወሰደው ሁለንተናዊ እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት ገልጿል፡፡በዛሬው ዕለትም በቤሩት በተመረጡ የሂዝቦላህ ይዞታዎች ላይ የተሳካ የአየር ላይ ጥቃት መፈጸሙን ጦር ባወጣው መግለጫ አመላክቷል፡፡በዚህም የሂዝቦላህ ደህንነት ሃላፊና የማዕከላዊ ም/ቤቱ ወሳኝ አባል ነቢል ኳዑክ መገደሉን ነው ያስታወቀው፡፡ በአንጻሩ በከፍተኛ አመራሩ መገደል ዙሪያ ሂዝቦላህ ያለው ነገር አለመኖሩን ቢቢሲ በዘገባው አስፍሯል፡፡እስራኤል በሂዝቦላህ ላይ እየወሰደች ባለው ወታደራዊ እርምጃ የቡድኑን መሪ ሀሰን ነስራላህን ባሳለፍነው አርብ መግደሏ ይታወሳል፡፡
Woreda to World
More Stories
የየመኑ ሃውቲ በማዕከላዊ እስራኤል “ወሳኝ ኢላማዎችን” በድሮኖች መትቻለሁ አለ
እስራኤል የተመድ ዋና ጸኃፊ ወደ ሀገሪቱ እንዳይገቡ እግድ ጣለች
ብራድፒት ነኝ በሚል ሁለት ሴቶችን 362 ሺህ ዶላር ያጭበረበረው ሰው