October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ነጥብ ተጋሩ

በ6ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል አቻ ተለያይተዋል፡፡ቀን 8 ሰዓት ከ30 ላይ በተደረገው ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ በዮስኮ ጋቫርዲዮል ጎል ቀዳሚ መሆን ቢችልም ከእረፍት መልስ አንቶኒ ጎርደን ፍፁም ቅጣት ምቱን ወደ ጎል ቀይሮ ባለሜዳዎቹን አቻ አድርጓል፡፡ውጤቱን ተከትሎ ማንቼስተር ሲቲ ፕሪሚየርሊጉን በ14 ነጥብ በጊዜያዊነት መምራት ሲችል ኒውካስል ነጥቡን ወደ 11 ከፍ በማድረግ 5ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡የሊጉ 6ኛ ሳምንት መርሃግብሮች መካሄዳቸውን ሲቀጥሉ አርሰናል ከሌስተር ሲቲ፣ብረንትፎርድ ከዌስትሃም፣ቼልሲ ከብራይተን፣ኤቨርተን ከክሪስታል ፓላስ፣ኖቲንገሃም ፎረስት ከፉልሃም እንዲሁም ወልቭስ ከሊቨርፑል ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡