October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ስራ ስኬታማነት እያንዳንዱ ባለድርሻ አካላት ሚናቸዉን በዘላቂነት እንዲወጡ ጥሪ ቀረበ።

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮያ ህዝቦች ክልል ሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ቢሮ “የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ዘርፍ ለወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ መሳለጥ የሚዲያዎች ሚና ከፍተኛ ነዉ” በሚል መሪ ቃል ከባለድርሻ አካላት ጋር በቦንጋ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካህዷል ። በመድረኩ የቢሮዉ ምክትል ሀላፊና የወሳኝ ኩነት ዘርፍ ሀላፊ አቶ ሰለሞን ደነቀ እንደገለጹት በርካታ ፋይዳዎችን የያዘዉ የወሳኝ ኩነቶች ምዝገባ ላይ እንደ ክልል በትኩረት እየተሰራ ነዉም ተብሏል።በቀጣይ እያንዳንዱ ኩነቶች ሙሉ በሙሉ በሚመዘገቡበት አኳኋን ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት በዘላቂነት በትኩረት እንዲሠሩ አሳስበዋል።