የካፌቾ ብሔረሰብ የቋንቋ እና የባህል ሲምፖዚየም በቦንጋ ከተማ እየተካሔደ ይገኛል፡፡ ሲምፖዚየሙ የብሔረሰቡን የዘመን መለወጫ በዓል ማሽቃሮ ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ነው።የማሽቃሮ በዓል በቦንጋ ከተማ በነገው ዕለት ይከበራል።ማሽቃሮ የዘመን መለወጫ በዓል የክረምቱ ወቅት አልፎ ብርሃናማው ጊዜ መግባቱ የሚበሰርበት ነው።የእርቅ፣ የሰላም እና የአንድነት መገለጫ በሆነው ማሽቃሮ ቀጣዩ ጊዜ የፍቅር እና የልማት እንዲሆን ሁሉም የብሔረሰቡ አባት ምርቃት የሚያገኙበት እንደሆነም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
EBC
More Stories
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በሩሲያ የድል በዓል የአቀባበል ስነ ስርዓት ላይ ተሳተፉ
አሜሪካዊው ሮበርት ፕሪቮስት የሮማ ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ሆነው ተመረጡ
የዘመኑን ዐርበኝነት እውን ለማድረግ ራስን ለመቻል በሚደረጉ የልማት ሥራዎች ዙሪያ-መለስ ትጋት ከኹሉም ዜጎች ይጠበቃል። -የኢፌዲሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት