የካፌቾ ብሔረሰብ የቋንቋ እና የባህል ሲምፖዚየም በቦንጋ ከተማ እየተካሔደ ይገኛል፡፡ ሲምፖዚየሙ የብሔረሰቡን የዘመን መለወጫ በዓል ማሽቃሮ ምክንያት በማድረግ የተዘጋጀ ነው።የማሽቃሮ በዓል በቦንጋ ከተማ በነገው ዕለት ይከበራል።ማሽቃሮ የዘመን መለወጫ በዓል የክረምቱ ወቅት አልፎ ብርሃናማው ጊዜ መግባቱ የሚበሰርበት ነው።የእርቅ፣ የሰላም እና የአንድነት መገለጫ በሆነው ማሽቃሮ ቀጣዩ ጊዜ የፍቅር እና የልማት እንዲሆን ሁሉም የብሔረሰቡ አባት ምርቃት የሚያገኙበት እንደሆነም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች ተናግረዋል።
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።