October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ 350 ለሚሆኑ በቴፒ ከተማ ለሚኖሩ አቅመ ደካማ ወገኖች የበዓል መዋያ ድጋፍ መበርከቱ ተገለጸ።

ድጋፉን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ያስተላለፋት የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ ይህ ዓይነቱ ድጋፍ ቀጣይነት እንዲኖረዉ ይሰራል ብለዋል።በጎ ፈቃደኛ ግለሰቦችንና የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን በማስተባበር 350 ለሚሆኑ ለተቸገሩ ወገኖች አዲሱን ዓመት ምክንያት በማድረግ ለእያንዳዳቸዉ የ 2 ሊትር ዘይትና የ4 ኪሎ ግራም ዱቄት ድጋፍ መበርከቱን የተናገሩት ደግሞ በቴፒ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽህፈት ቤት የሴቶች ሊግ ሀላፊ ወይዘሮ ይጋርዱ ጤናዉ ናቸዉ። በተመሳሳይ በከተማዉ መዋቅር ዉስጥ የሚሰሩና ከ2 ሺህ ብር በታች የሚከፈላቸዉ 126 ደመወዝተኞችም ለእያንዳንዳቸዉ የ5 ሊትር ዘይት ድጋፍ ተሰጥቷቸዋል። ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ።