ዮርዳኖስ ከዌስትባንክ ጋር በሚያዋስናት የድንበር መተላለፊያ የተፈጸመውን ጥቃት እየመረመርኩ ነው ብላለች
ሶስት እስራኤላውያን በዮርዳኖስ እና ዌስትባንክ መተላለፊያ ድንበር ተተኩሶባቸው ተገደሉ።
እያሽከረከረ ከወደ ዮርዳኖስ ወደ ዌስትባንክ የገባው ግለሰብም በጸጥታ ሃይሎች መገደሉን የእስራኤል ባለስልጣናት ተናግረዋል።
ህይወታቸው ያለፈው እስራኤላውያን እድሜያቸው ከ50 አመት በላይ የሆነ ወንዶች መሆናቸውን የእስራኤል አስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት ተቋም ገልጿል።
ዮርዳኖስ “አለንቢ” በተሰኘው መተላለፊያ የተፈጸመውን ግድያ እየመረመርኩ ነው ማለቷን የሀገሪቱ ብሄራዊ የዜና ወኪል ፔትራ ኒውስ አስነብቧል።
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ግድያውን አጥብቀው ያወገዙት ሲሆን፥ ከኢራን እና ከምታስታጥቃቸው ሃይሎች ጋር የሚገናኝ ጥቃት ነው ብለዋል።
Al-Ain
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች