የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ በግብርናው ዘርፍ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተፕራይዞችን ለማደራጀት እና ወደ ስራ ለማስገባት ተስማምተዋል፡፡ ስምምነቱን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል እና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር) ተፈራርመውታል፡፡ ሚኒስቴሩ ሥራ ፈጣሪዎችን በማበረታታት ኢኮኖሚያዊ ዕድገትን ለማረጋገጥ ከባንኩ ጋር በትብብር እየሰራ መሆኑን ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል ተናግረዋል፡፡ “በግብርናው ዘርፍ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች በበቂ መጠን የሉም” ያሉት ሚኒትሯ፤ ስምምነቱ በመስኩ የበለጠ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር እንደሚያስችል ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ባንኩ ከሚኒስቴሩ ጋር በመሆን በተያዘው በጀት ዓመት ወጣቶችን ወደ ስራ ለማስገባት አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጉን አስታውቀዋል፡፡ ለመርሐ-ግብሩ በአጠቃላይ 43 ሚሊዮን ዶላር ሥራ ላይ እንደሚውል የገለጹት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር)፤ ባንኩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ፋይናንሱን ተደራሽ እንደሚያደርግ አብራርተዋል። የአፍሪካ ልማት ባንክ ለስራ ዕድል ፈጠራ ፋይናንስ የሚያቀርብ ሲሆን በኢትዮጵያ ልማት ባንክ በኩል ለአነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ተደራሽ እንደሚሆን መገለጹን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።