ሰልፈኞቹ የኔታንያሁ አስተዳደር ቀሪዎቹን 101 ታጋቾች እንዲያስለቅቅ ጠይቀዋልበጋዛ ስድስት ታጋቾች መገደላቸውን ተከትሎ እስራኤላውያን ቁጣቸውን በአደባባይ እያሰሙ ነው።የኔታንያሁ አስተዳደር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ደርሶ ታጋቾችን ማስለቀቅ አልቻለም ያሉ 500 ሺህ የሚገመቱ ሰልፈኞች በቴል አቪቭ፣ እየሩሳሌምና ሌሎች ከተሞች ድምጻቸውን አሰምተዋል።ሰልፈኞቹ በእየሩሳሌም መንገድ ዘግተው በጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ መኖሪያ ቤት ዙሪያ ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ውለዋል።የቴል አቪቭ ጎዳናዎችም የሟቾቹን ታጋቾች ምስሎች በያዙ ሰልፈኞች ተሞልተው መዋላቸውን ነው ሬውተርስ ያስነበበው።ሰልፈኞቹ የኔታንያሁ አስተዳደር ቀሪዎቹን 101 ታጋቾች ለማስለቀቅ በፍጥነት የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደርስ ጠይቀዋል።
Al-Ain
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።