የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለሀገር ዕድገት እና ብልፅግና ወሳኝ ድርሻ አለው ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አሕመድ ሺዴ ገለጹ፡፡
አቶ አሕመድ ሺዴ በቅርቡ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን በተመለከተ ከኢፌዴሪ አየር ኃይል የተለያዩ ክፍሎች ከተውጣጡ የሰራዊቱ አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡
በመድረኩ በሰጡት ማብራሪያ÷ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም ከማስጠበቁም ባለፈ የዜጎችን ተጠቃሚነት ያረጋግጣል ብለዋል።
ይህም የኢትዮጵያን ዕድገት እና ብልፅግናን ወደ ተሻለ ከፍታ እንደሚያሸጋግር ተናግረዋል።
የኢፌዴሪ አየር ኃይል አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው÷ በተቋሙ ያሉ የሰራዊቱ አመራሮች የመንግስትን የኢኮኖሚ ፖሊሲ በበቂ ሁኔታ መረዳታቸው ቀጣይ ተልዕኳቸውን በብቃት እንዲመሩ እንደሚያስችል መጥቀሳቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ማህበራዊ ትስስር ገጽ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።