የባህላዊ ትውፊትና የጥበብ ማህደር በሆነችው አክሱም የሚገኙ የቱሪስት መስህቦችን፣ ባህላዊና ሕዝባዊ በዓላት ትውፊታቸውን ሳይቀይሩ በማልማት ወደ ሕዝባዊ ጥቅም እንቀይርቸዋለን ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳ ገለጹ። በአክሱም ከተማና አካባቢው የዓይኒዋሪ የልጃገረዶች በዓል የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታቸው ረዳን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች እና በኢትዮጵያ የጣልያን አምባሳደር በተገኙበት በድምቀት እየተከበረ ይገኛል። ከአክሱም ከተማና ከማዕከላዊ ዞን ሁሉም ወረዳዎች የተውጣጡ የዓይኒዋሪ ልጃገረዶች የተለያዩ አልባሳት ለብሰውና በጌጣጌጥ ደምቀው በዓሉን እያከበሩ ናቸው። ዛሬ በተጀመረው በዚሁ በዓል ላይ አቶ ጌታቸው ረዳ እንደገለጹት፤ የአክሱም ልጃገረዶች ዓይኒዋሪን በዓል ከዘመን ዘመን በቅብብሎሽ ሲያከብሩትና ሲያደምቁት ቆይተዋል። አክሱም የባህላዊ ትውፊትና የጥበብ ማህደር መሆኗን ጠቁመው፤ ለቀጣይም የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ ልንሰራ ይገባናል ብለዋል።
EBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ