በስልጤ ዞን ሰሞኑን በተከሰተው የጎርፍ አደጋ የተፈናቃይ ቁጥር እየጨመረ በመሆኑ እየተደረገ ያለው ሰብዓዊ ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የዞኑ አደጋ ስጋትና ስራ አመራር ጽ/ቤት ጥሪ አቅርቧል፡፡ የፅ/ቤቱ ኃላፊ ወሲላ አሰፋ ለኢቢሲ ሳይበር እንደገለፁት፤ በጎርፉ አደጋው 7ሺ ሰዎች ተፈናቅለዋል፤ 1300 ሄክታር መሬት ማሳ ከጥቅም ውጭ ሆኗል፤ 6 ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 1ሺ ቤቶች በጎርፍ ተውጠዋል፡፡ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን በስልጢ እና ምስራቅ ስልጢ ወረዳዎች በደረሰው የጎርፍ አደጋ እየተፈናቀሉ ያሉ ሰዎች ቁጥር አሁንም እየጨመረ መሆኑን ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡ በሁለቱ ወረዳዎች በጎርፍ ተውጠው የነበሩ ቀበሌዎች ከ6 ወደ 8 ማደጋቸውንና በውሃ የተዋጡ ትምህርት ቤቶች ቁጥር 6 መድረሱን ተናግረዋል፡፡
በስልጤ ዞን በጎርፍ አደጋው የተፈናቀሉ ሰዎች ቁጥር 7ሺህ ደርሷል፡- የዞኑ የአደጋ ስጋትና ስራ አመራር ጽ/ቤት

More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።