የኢትዮጵያ ስፖርት አሁን ከገባበት የውጤት ቀውስ ለማውጣት ጊዜያዊ ጥገና ወይም ጊዜያዊ የህመም ማስታገሻ ሳይሆን ስር ነቀል ለውጥ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የቀድሞው የኢትዮጵያ ሞተር ስፖርት ማህበር ፕሬዝንት አቶ አስራት ወርቁ ገለፁ፡፡ የሀገሪቱ ስፖርት ታሟል የሚሉት አቶ አስራት፤ ስፖርቱ አሁን ካለበት ችግር ለማውጣት ስር ነቀል ለውጥ በማድረግ ስፖርቱን ለመታደግ የመንግስት እይታና ጣልቃ ገብነት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል፡፡ የሀገሪቱን የስፖርት ፖሊሲ ከማስተካከል፤ ለስፖርት ኢንቨስትመንት አስፈላጊውን ድጋፍና ጥቅማጥቅም ከማድረግ፤ አጋር አካላት ለስፖርት እድገት የሚያወጡት ወጪ እንደ ወጪ ተይዞላቸው ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ከማድረግ፤ ሀገሪቱ ያላት አቅም በሙሉ በመጠቀም ስፖርት በማሳደግ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንድትሆን የመንግስት ሚና ወሳኝ ነው ብለዋል አቶ አስራት ወርቁ ፡፡ ስፖርት ጤናማና አምራች ትውልድ በመገንባት ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ቁልፍ ሚና መጫወት ይችላል ያሉት አቶ አስራት፤ የሀገሪቱ ስፖርት ታሞ ቃሬዛ ላይ ነው፤ መንግስት በስፖርት ላይ ስር ነቀል ለውጥ ወይም አብዮት ማካሄድ አለበት ብለዋል፡፡
Woreda to World
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።