የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ እንዳሉት÷ የተቀላጠፈና አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው፡፡በተጠናቀቀው 2016 በጀት ዓመት 427 ሺህ በላይ አዳዲስ ደንበኞችን ማፍራት መቻሉን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል፡፡በ2016 በጀት ዓመት በከተለያዩ የገቢ ምንጮች 42 ቢሊየን ብር ገቢ ማግኘት መቻሉንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ችግርን ለመቅረፍም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመሮችን አቅም የማሳደግ፣ የመፈተሽና የመጠገን ሥራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አመልክተዋል፡፡
Woreda to World
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ