ኢትዮጵያ የአማኝ ህዝቦች ሀገር ናት፡፡ ሁሉም ዜጋ ሊባል በሚችል ደረጃ ስለራሱ፣ ስለቤተሰቡ፣ ስለሀገሩ እና በቀጣዩ ዓለም ስላለው ዕጣ ፈንታ ወደ ፈጣሪው ይጸልያል፡፡ በየቤተ- ዕምነቱ ያለው ምዕመን ከፈጣሪው ጋር ያለውን ሕብረት ለማጠንከር በጾም፣ በስግደት እና በምጽዋት ይተጋል፡፡ የኃይማኖት አባቶች ቅዱሳን መጻሕፍትን እየገለጡ ለስጋም ለነፍስም የሚበጀውን የፈጣሪን ቃል ያስተምራሉ፡፡ ዝማሬው፣ ሕብረቱ፣ ስብከቱ፣ ተግሳጹ….ሁሉም በቦታው እንዳለ ነው፡፡ እጆች ለጸሎት ለመዘርጋት ሳይሰንፉ፣ ዓይኖች ለምሕረት ለማንባት ሳይደርቁ፣ ጆሮዎች ቃሉን ለማድመጥ ሳይሞሉ፣ እግሮች ለመንበርከክ ሳይዝሉ፤ ትውልዱ ከሥነ-ምግባር እሴቶች ገሸሽ እያለ የመምጣቱ ነገር ለብዙዎች ግራ ነው፡፡ ኢቢሲ ሳይበር የሥነ-ምግባር እና ግብረ-ገብ እሳቤዎችን አስመልክቶ የኃይማኖት መምህራንን አነጋግሯል፡፡
የሚያስተምር አባት፣ የሚሰማ ምዕመን

More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ