ችግሩ መፍትሔ ለማበጀት ከሸካ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መምሪያ ጋር እየተሰራ መሆኑንም ወረዳው አሳውቋል። በሸካ ዞን ማሻ የምርጫ ጣቢያ ተመራጭ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባልና የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ አዝመራ አንደሞና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ጉብኝት ተደርጓል። የሬድዮ ጣቢያችን የሸካ ዞን ከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን መምሪያ ምክትል ኃላፊ አቶ ካዳኔ ከሲቶ በስልክ በስልክ በሰጡት መረጃ አራት ብሎክ ያለው የጤና ጣቢያዉ በ2008 ዓ.ም ግንባታው የተጀመረ ሲሆን ስራው ያስጀመረው ኮንትራክተር ስራ በማቋረጡ ምክንያት ተጓቶ መቆየቱን አንስተው አሁን ላይ ከአድስ ኮንትራክተር ጋር በመሆን የተለያዩ ማሻሻያዎችን በማድረግ ግንባታው ወደ መጠናቀቁ ደረጃ መድረሱን ገልጸዋል።
ዘጋቢ ሀና ግርማ
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።