በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የተመራ ልዑካን ቡድን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደርን የስራ እንቅስቃሴ ጎብኝቷል፡፡ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሃሚድ ሀገራዊ የሳይበር ደህንነትን ለማረጋገጥ በተቋሙ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን አስመልክቶ ለቡድኑ ገለጻ አድርገዋል። በሳይበር ደህንነት ዘርፍ በሁለቱ ሀገራት መካከል የተጀመረውን ሁሉን አቀፍ የትብብር ስራ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እንደሚሰራም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌኒ ተረክሂን የጉብኝቱ ዓላማ የኢትዮጵያን የሳይበር ደህንነት ልምድ መመልከትና ሁለቱ ሀገራት በዘርፉ ያላቸውን ትብብር ማጠናከር መሆኑን አመልክተዋል። ኢትዮጵያ በሳይበር ደህንነት ዘርፍ፤ በተለይም ደግሞ የቴክኖሎጂና የዕውቀት ባለቤትነትን በማረጋገጥ ረገድ ከፍተኛ ስራ መስራቷን ከጉብኝቱ መረዳታቸውን ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነቷን እና ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ በምታደርገው ጥረት ሩሲያ ያላትን ልምድ ከማካፈል ጀምሮ በጋራ ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት አምባሳደሩ መናገራቸውን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።