በአቅርቦት እጥረት ምክንያት ለመጪው በዓል በሚውሉ ምርቶች ላይ የዋጋ መናር እንዳይፈጠር በቂ ዝግጅት መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ከ115 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ጅቡቲ መድረሱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በቀናት ውስጥ ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ነው የጠቆሙት፡፡አክለውም ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ጠቅሰዋል፡፡ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል እንዳይጎዳ መንግስት በጥንቃቄ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ስራው ውጤታማነት እያሳየ መሆኑን ገልጸው፣በምርት በእጥረት ምክንያት የሚፈጠር የዋጋ ንረት እንደማይኖር ነው የተናገሩት፡፡
EBC
More Stories
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው