በአቅርቦት እጥረት ምክንያት ለመጪው በዓል በሚውሉ ምርቶች ላይ የዋጋ መናር እንዳይፈጠር በቂ ዝግጅት መደረጉን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ገልፀዋል፡፡ከ115 ሚሊዮን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት ጅቡቲ መድረሱን የገለጹት ሚኒስትሩ፤ በቀናት ውስጥ ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ነው የጠቆሙት፡፡አክለውም ሌሎች መሰረታዊ የፍጆታ ምርቶች ወደ ምርት ማዕከል እንደሚገቡም ጠቅሰዋል፡፡ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል እንዳይጎዳ መንግስት በጥንቃቄ እየሰራ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ስራው ውጤታማነት እያሳየ መሆኑን ገልጸው፣በምርት በእጥረት ምክንያት የሚፈጠር የዋጋ ንረት እንደማይኖር ነው የተናገሩት፡፡
EBC
More Stories
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ የአዳር ትምህርት ተመቻችቶ የመማር ማስተማር ስራ መጀመሩ የበለጠ ውጤት እንድናስመዘግብ አግዞናል ሲሉ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ የአዳር ትምህርት እድል ያገኙ ተማሪዎች ገለፁ ።