October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢትዮጵያ እና የኬኒያ የመረጃ ተቋማት የሽብር ቡድን አመራሮች እና ታጣቂዎች ላይ የጀመሩትን ኦፕሬሽን አጠናክረው ለመቀጠል ተስማሙ

የኢትዮጵያ እና የኬኒያ የመረጃ ተቋማት በድንበር አካባቢ እና በኬኒያ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ የሽብር ቡድን አመራሮች እና ታጣቂዎች ላይ የጀመሩትን ኦፕሬሽን አጠናክረው ለመቀጠል አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ በኬኒያ የመረጃ አገልግሎት ዳይሬክተር ጄነራል ኑረዲን መሐመድ ሀጂ የተመራ የልዑካን ቡድን ለሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ ዳይሬክተር ጄነራሉ ከሉዕካን ቡድናቸው ጋር ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደረሱ የብሄራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ዳይሬክተር ጀነራል አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና የአገልግሎት መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች አቀባበል አድርገውላቸዋል።

EBC