ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ በመሬት መንሸራተት አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ25 ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡ ድጋፉን ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን በመወከል አቶ ያዕቁብ ፈቂ፤ ለጎፋ ዞን ዋና አሰተዳደሪ ዳግማዊ አየለ (ኢ/ር) አስረክበዋል፡፡ ከድጋፉ ውስጥ 10 ሚሊየን ብር ለተጎጂዎች አፋጣኝ እርዳታ፣ 15 ሚሊየን ብር ደግሞ አካባቢውን በዘላቂነት ለማልማት የሚውል መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ ዋና አስተዳዳሪው ለተደረገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበው፤ ተጎጂዎችን በዘላቂነት መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለው ድጋፉ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በዞኑ በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ የተሰማውን ሐዘን በድጋሚ ገልጾ ለተጎጂዎች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።