የሀገር መከላከያ ሠራዊት የሀገርን ሉዓላዊነት እና ሰላም ከማረጋገጥ ባለፈ በልማቱ ላይ እያደረገ ያለው ተሳትፎ አበረታች ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር ) ገለጹ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር ) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ እንደገለጹት ÷መከላከያ ሠራዊት የሰላም ምንጭ ብቻ ሳይሆን የልማት እና የፈጠራ ምንጭ መሆን ስላለበት በዚህ አግባብ እየተመራ እየተገኘ ያለው ውጤት ተስፋ ሰጭ ነው ፡፡ይህም ተስፋ ሰጭ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል ነው ያሉት ።በስንዴ ምርት በእርሻ በ #አረንጓዴዓሻራ ብዙ የኢንዱስትሪ ውጤቶችን በማምረት ልማቱን ለማሳለጥ እና የብልፅግና መሰረት ለመጣል እያደረገ ያለው ጥረት ሊበረታታ እንደሚገባም ገልጸዋል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።