አባስ በዛሬው እለት በቱርክ ፓርላማ በመገኘት በፍልስጤም ወቅታዊ ሁኔታ ገለጻ ያደርጋሉየፍልስጤም አስተዳደር ፕሬዝዳንት ማህሙድ አባስ በአንካራ ከቱርኩ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ጋር ተወያዩ።በዝግ የተካሄደው ምክክር “እስራኤል በፍልስጤማውያን ላይ እየፈጸመችው ባለው ጭፍጨፋ እና ዘላቂ የተኩስ አቁም ስምምነት ለመድረስ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነበር” ብሏል የፕሬዝዳንት ኤርዶሃን ጽህፈት ቤት።እስራኤል በሃማስን የጥቅምት 7 ጥቃት ተከትሎ በጋዛ የምትፈጽመውን ጥቃት አጥብቀው የሚቃወሙት ኤርዶሃን፥ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁንን ከአዶልፍ ሂትለር ጋር እስከማመሳሰል መድረሳቸው ይታወሳል።አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት በሽብርተኛ ድርጅትነት የመዘገቡትን ሃማስም “የነጻነት ታጋይ” ነው በማለት ማወደሳቸውም አይዘነጋም።
Al-Ain
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት ጉዳይ ንግግር ለመጀመር አጥጋቢ እቅድ እንዳልደረሳት ገለጸች