October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በቡና ጥራትና ህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ስርዓት ላይ በትኩረት እንዲሰራ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ ጥሪ አቀረቡ ።

በዞኑ በ2017 የምርት ዘመን የቡና አቅርቦትና ጥራትን ለማሳደግ ብሎም ህገ ወጥ ንግድን ለመከላከል ከባለድርሻ አካለት ጋር የንቅናቄ መድረክ በቴፒ ከተማ አካሄዷል።በመድረኩ የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አበበ ማሞ እንደለጹት ዞኑ ዕምቅ የቡና ሀብት ያለዉ ቢሆንም በጥራት ማነስና በህገ ወጥ ንግድ መበራከት በየዓመቱ ለማዕከላዊ ገበያ የምቀርበዉ ምርት እየቀነሰ መምጣቱን ተናግረዋል።ለአብነትም በ2015 የምርት ዘመን 18 ሺህ የቀረበ መሆኑንና ይህም በ2016 ምርት ዘመን ወደ 14 ሺህ ቶን ዝቅ ማለቱን ዋና አስተዳዳሪዉ አንስተዋል። በ2017 የምርት ዘመን ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረብ እንደሚገባ ያነሱት ዋና አስተዳዳሪዉ ቡና ለሀገራችን የዉጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ በመሆኑ በጥራትና በህገ ወጥ ንግድ ቁጥጥር ላይ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ያለድርድር በትኩረት እንዲሰሩ አሳስበዋል።የሸካ ዞን ግብርና ፣ አካባቢ ጥበቃና ህብረት ሥራ መምሪያ ኃላፊ አቶ አእምሮ ደሳልኝ ዞኑ ካለዉ የቡና ሽፋንና ምርት አንጻር ለማዕከላዊ ገበያ እየቀረበ ያለዉ ቡና በጥራት ማነስና በህገ ወጥ ንግድ ምክንያት በየዓመቱ እየቀነሰ በመምጣቱ ለዚህም የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ከባለድርሻ አካላቱ እንዲረባረቡ ጠይቀዋል።ዘጋቢ ጌትነት ገረመዉ