በደጋማው አካባቢ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በጎግ፣ በላሬ፣ በጆር እና በዋንቱዋ ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎች ላይ የጎርፍ መጥለቅለቅ መከሰቱን የጋምቤላ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራር አስታወቀ፡፡
በተከሰተው የጎርፍ አደጋም ከ16 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን እና ለጊዜው ደረቃማ በሆኑ አካባቢዎች እንዲሰፍሩ መደረጉ ተጠቅሷል፡፡
ከክልሉ መንግሥትና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት በመነጋገር ለተፈናቃዮቹ አፋጣኝ ድጋፍ የሚደርስበት ሁኔታ እንደሚመቻችም ተጠቁሟል፡፡
የጎርፍ አደጋው በቤት ውስጥ ያሉ ቁሳቁሶችን ጨምሮ በቁም እንስሳትና ሰብል ላይ ጉዳት ማድረሱን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
ሀገራዊ የጤና ፖሊሲ ከመከላከልባሻገር አክሞ መዳንን መሰረት ያደረገ ስራን መስራት እንደሚገባ ተገለፀ።
በኢራን ወደብ በደረሰ ፍንዳታ 25 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ