በፓሪስ 2024 የኦሊምፒክ ወድድር በማራቶን ኢትዮጵያ በአትሌት ታምራት ቶላ አማካኝነት የመጀመሪያ ወርቋን አግኝታለች፡፡
በፓሪስ ኦሊምፒክ የወንዶች የማራቶች ውድድር የተካሄደ ሲሆን ÷አትሌት ቀነኒሳ በቀለ፣ ታምራት ቶላና ደሬሳ ገሌታ ኢትዮጵያን ወክለው ተወዳድረዋል።
በዚህም ታምራት ቶላ ውድድሩን 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ26 ሰከንድ በመግባት በቀዳሚነት በማጠናቀቅ በኦሊምፒኩ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል፡፡
አትሌት ደሬሳ ገለታ ደግሞ ውድድሩን በአምስተኛ ደረጃ አጠናቋል፡፡
More Stories
ማንቼስተር ሲቲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ነጥብ ተጋሩ
በፕሪሚየር ሊጉ አዳማ ከተማ ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸነፈ
በ5 ሺህ ወንዶች ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከአንድ እስከ ሶስት ተከታትለው ገቡ