በሀረሪ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በይፋ ተጀምሯል።
ክልላዊ የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፉ ከዛሬ ጀምሮ ለተከታታይ 6 ቀናት የሚቆይ ነው።
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር ዶ/ር ተገኘወርቅ ጌጡ የምክክር ሂደቱ ለኢትዮጵያ ተስፋን በማለምለም ችግሮችን ከግጭት ይልቅ በውይይት የመፍታት ባህል የሚጎለብትበት እንደሆነ ገልፀዋል።
በመድረኩ የተለያዩ የማህበረሰብ ወኪሎች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሶስቱ የመንግሥት አካላት ወኪሎች፣ የተለያዩ ማህበራት እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪዎች እየተሳተፉ ነው።
በአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መድረኩ ክልላዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ሀሳቦችና አጀንዳዎች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
EBC
More Stories
በ2016 የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ የ8 ነጥብ 1 በመቶ ዕድገት አስመዝግቧል- ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር)
ሙስና የተበላሸ አስተሳሰብ፣ ባህልና አሰራር ውጤት ነው – ም/ጠ/ሚ ተመስገን ጥሩነህ
የሸካ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤቶች የ2017 በጀት ዓመት የዳኞች መደበኛ ስራ የማስጀመሪያ ውይይት መድረክ በማሻ ከተማ አካሂዷል።