ከቀጣይ ሣምንት ጀምሮ ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በመላ ሀገሪቱ እንደሚሠራጭ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ የተለያዩ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች ዛሬ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ሕግ መጨረሳቸውንም ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ምርቱ ለገበያው በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ በመወያየት የመፍትሔ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል፡፡በዚህም መሠረት የገበያ ሁኔታን በዘላቂነት ለማረጋጋጥ በመንግሥት ወጭ የተገዛው ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሣምንት በመላ ሀገሪቱ ይሠራጫል ብለዋል፡፡ 468
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።