ከቀጣይ ሣምንት ጀምሮ ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በመላ ሀገሪቱ እንደሚሠራጭ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) አስታወቁ፡፡በአዳማ ጉምሩክ ጣቢያ የተለያዩ መሰረታዊ ሸቀጦችን ጭነው የቆሙ ከ700 በላይ ተሽከርካሪዎች ዛሬ የጉምሩክ ሥነ-ሥርዓት ሕግ መጨረሳቸውንም ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ምርቱ ለገበያው በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ በመወያየት የመፍትሔ አቅጣጫ መቀመጡንም ጠቁመዋል፡፡በዚህም መሠረት የገበያ ሁኔታን በዘላቂነት ለማረጋጋጥ በመንግሥት ወጭ የተገዛው ከ14 ሚልየን ሊትር በላይ የምግብ ዘይት በሚቀጥለው ሣምንት በመላ ሀገሪቱ ይሠራጫል ብለዋል፡፡ 468
FBC
More Stories
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ የአዳር ትምህርት ተመቻችቶ የመማር ማስተማር ስራ መጀመሩ የበለጠ ውጤት እንድናስመዘግብ አግዞናል ሲሉ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ ልዩ የአዳር ትምህርት እድል ያገኙ ተማሪዎች ገለፁ ።