October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ትራምፕ ሁለተኛውን ዙር የምርጫ ክርክር ከካማላ ሃሪስ ጋር ለማድረግ ተስማሙ

በፎክስ ኒውስ አዘጋጅነት በሚካሄደው የምርጫ ክርክር ላይ ተመልካቾች እንዲታደሙ ተፈቅዷል

ሁለተኛው ዙር ክርክር የምርጫውን አሸናፊነት ይወስናሉ ከሚባሉ ግዛቶች መካከል አንዷ በሆነችው ፔንሴልቬንያ ይካሄዳል

የሪፐብሊካኑ እጩ ዶናልድ ትራምፕ ባይደንን ተክተው የዴሞክራት እጩ እንደሚሆኑ ከሚጠበቁት ካማላ ሃሪስ ጋር በሁለተኛው ምርጫ ክርክር ለመሳተፍ ተስማምተዋል፡፡

በአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ የተካሄደው የመጀመርያ ዙር ክርክር የባይደንን የዴሞክራት እጩነት አስከፍሏል፡፡ 

በሲኤንኤን አዘጋጅነት ያልተመልካች በዝግ ስቱድዮ በተደረገው ክርክር ሀሳባቸውን በቅጡ መግለጽ ሲሳናቸው የታዩት ጆ ባይደን ከእጩነት እንዲነሱ ተቃውሞ በርትቶባቸው ከምርጫው እራሳቸውን ማግለላቸው የሚታወስ ነው፡፡

ለ90 ደቂቃ በተካሄደው ክርክር ዶናልድ ትራምፕ አንዳንድ ከእውነታነት ከራቁ ሃሳቦቻቸው ጭምር በባይደን ላይ ብልጫ እንደወሰዱ ብዙዎች ተስማምተዋል፡፡