October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በ1 ሺህ 500 የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኤርሚያስ ግርማና ሳሙኤል ተፈራ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፉ

በ33ኛው ኦሊምፒክ ጨዋታዎች የ1 ሺህ 500 ሜትር የወንዶች ማጣሪያ ውድድር ኤርሚያስ ግርማ እና ሳሙኤል ተፈራ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አልፈዋል፡፡በምድብ ሁለት የተወዳደረው ኤርሚያስ 3 ደቂቃ ከ35 ሴኮንድ ከ21 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ነው ውድድሩን በቀዳሚነት በማጠናቀቅ ለግማሽ ፍፃሜ የበቃው፡፡በተመሳሳይ በምድብ ሶስት በዚሁ ርቀት የተወዳደረው ሌላኛው አትሌት ሳሙኤል ተፈራ 3 ደቂቃ ከ37 ሴኮንድ ከ34 ማይክሮ ሴኮንድ በመግባት ስድስተኛ ደረጃን በመያዝ ወደ ግማሽ ፍጻሜው የገባው።በምድብ አንድ የተወዳደረው አትሌት አብዲሳ ፈይሳ 14ኛ ደረጃን በመያዝ ማጣሪያውን ሳያልፍ ቀርቷል፡፡