የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡን በቁንጽል ሳይሆን በምልዐት መመልከት ይገባል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አስገነዘቡ፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳሉት፥ የማክሮ ኢኮኖሚ ለውጡን በቁንጽል ሳይሆን በምልዐት መመልከት ይገባል። በመደመር ዕሳቤያችን ለሀገር ልማት ምን መደረግ እንዳለበት በጥልቀት መዝነን አስቀምጠናል ያሉ ሲሆን፥ ዓላማችን የኢትዮጵያን ብልጽግና ማረጋገጥ ነው ብለዋል፡፡አካሄዳችን ድሃ ተኮር፤ ትኩረታችን ለችግር በመጠቃት ተጋላጭ የሆኑ ደካሞችን መደገፍ ነው ሲሉም ነው የገለጹት። የለውጥ ሥራዎቻችን ሁሉ ስኬት በባለድርሻ አካላት የተባበረ ጥረት ላይ ይመሠረታል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ ይህም ምርታማነትን፣ የውጭ ንግድንና ገቢን ተባብሮ ማሳደግ ማለት እንደሆነ አንስተዋል፡፡የሕግ አስፈጻሚ አካላት የለውጥ ሥራውን ባልተገባ ሕገ-ወጥ መንገድ ለመጠቀም በሚፈልጉ ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ኃላፊነት እንደተሰጣቸውም ነው የገለጹት። እነዚህን ሃሳቦችም ዛሬ ጠዋት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በነበራቸው መድረክ መግለጻቸውን ጠቅሰው፥ የበለጠ ዝርዝር መረጃ ለማግኘት የመድረኩን ውይይት በሚዲያዎች መከታተል እንደሚቻል አመላክተዋል።
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።