በጀርመን አስተናጋጅነት ሲካሄድ የቆየው 17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ በስፔን አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ በበርሊን ኦሊምፒክ ስታዲየም በተካሄደው የፍጻሜ ጨዋታ ስፔን እንግሊዝን 2 ለ 1 በማሸነፍ ለአራተኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት ሆናለች፡፡ በጨዋታው የስፔንን የማሸነፊያ ግቦች ኒኮ ዊሊያም እና ማይክል ኦያርዛባል በ47ኛው እና በ86ኛው ደቂቃ አስቆጥረዋል፡፡ እንግሊዝን ከሽንፈት ያልታደገችውን ብቸኛ ግብ ተቀይሮ የገባው ኮል ፓልመር በ73ኛው ደቂቃ አስቆጥሯል፡፡ በውድድሩ አስደናቂ ብቃት ሲያሳይ የቆየው የ17 ዓመቱ ኮከብ ላሚን ያማል በዚህም ጨዋታ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ በማቀበል ውድድሩን በስኬት አጠናቋል፡፡
EBC
More Stories
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሊቨርፑል ከአስቶን ቪላ ጋር ይጫወታሉ
የቀድሞው የሪያል ማድሪድ ኮከብ ማርሴሎ ጫማ ሰቀለ
አርሰናል ከካራባኦ ዋንጫ ተሰናበተ