October 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በመደመር እሳቤ ዙሪያ ለአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ገለፃ ተደረገ

ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ስልጠና በዛሬው ዕለት በመደመር ትውልድ እና የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ አንኳር መርሆዎች ላይ አተኩሮ ተካሂዷል። በመደመር መንገድ በውጭ ግንኙነት ስራዎች ባለፉት አመታት በተገኙ ስኬቶች እና የተግባር ለውጦች ዙሪያ ለአምባሳደሮቹ ገለፃ ተደርጓል። መደመር አገር በቀል እሳቤ መሆኑን በመገንዘብ በዲፕሎማሲው መስክ ሃገራዊ ክብርን እና ጥቅምን ለማስጠበቅ በትጋት ሊሰራ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ ዓለምአቀፍ አሰላለፍን በመገንዘብ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን በማስቀደም መሰረታዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መድረኩን በአወያይነት መምራታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

EBC