ሶስተኛ ቀኑን የያዘው የአዲስ ተሿሚ አምባሳደሮች ስልጠና በዛሬው ዕለት በመደመር ትውልድ እና የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ አንኳር መርሆዎች ላይ አተኩሮ ተካሂዷል። በመደመር መንገድ በውጭ ግንኙነት ስራዎች ባለፉት አመታት በተገኙ ስኬቶች እና የተግባር ለውጦች ዙሪያ ለአምባሳደሮቹ ገለፃ ተደርጓል። መደመር አገር በቀል እሳቤ መሆኑን በመገንዘብ በዲፕሎማሲው መስክ ሃገራዊ ክብርን እና ጥቅምን ለማስጠበቅ በትጋት ሊሰራ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል። የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፓሊሲ ዓለምአቀፍ አሰላለፍን በመገንዘብ ከፉክክር ይልቅ ትብብርን በማስቀደም መሰረታዊ ጥቅሞችን ለማስጠበቅ የሚያስችል መሆኑ ተብራርቷል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ መድረኩን በአወያይነት መምራታቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።