የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 54 ሺህ 795 ሜትሪክ ቶን የታጠበና ያልታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ ማቅረቡን አስታወቀ፡፡
አጠቃላይ አቅርቦቱም ካለፈው በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃርም የ28 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱን ነው የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር ኢ/ር) በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ያስታወቁት፡፡
እየተሻሻለ የመጣው የቡና ማሳ እንክብካቤ፣ በክልሉ የቡና ቅምሻና ሰርቲፊኬሽን ማዕከል ሥራ መጀመር፣ የኮንትሮባንድ ንግድ ቁጥጥር መጠናከር እንዲሁም በግብይት ሂደት ያጋጥሙ የነበሩ ማነቆዎችን መፍታት መቻሉ ለምርት ዕድገቱ አስተዋፅኦ ማበርከቱንም አብራርተዋል፡፡
በ2017 የበጀት ዓመትም ጥራቱን የጠበቀ ቡና ለገበያ ለማቅረብ በተሻለ አቅም እና ተነሳሽነት መሥራት እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።