October 5, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ከታክስ ዕዳ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ ተሰበሰበ

 በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከታክስ ዕዳ ከ49 ቢሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን ገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡

ከታክስ ዕዳ 41 ቢሊየን 662 ሚሊየን 896 ሺህ 213 ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ 49 ቢሊየን 664 ሚሊየን 299 ሺህ 370 ብር መሰብሰቡን ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

ከፍተኛ የታክስ ዕዳ መጠን ያለባቸውን ታክስ ከፋዮች በመለየት ቅድሚያ ተሰጥቶ መሠራቱና ለዋና መስሪያ ቤት በልዩ ሁኔታ እንዲታዩ የሚቀርቡ ጥያቄዎችን ፈጥኖ ምላሽ መስጠቱ ለዕቅዱ መሳካት ማገዙ ተገልጿል፡፡

ከተሰበሰበው የታክስ ዕዳ ውስጥ 30 ቢሊየኑ 30 ቀን ካልሞላው የታክስ ዕዳ መሰብሰቡን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል፡፡

FBC