በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃን ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር ኢ/ር) ገለጹ፡፡
የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከአጋር አካላት ጋር በመተባበር “በተግዳሮቶች ፊት መፅናት” በሚል መሪ ሃሳብ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና ተደራሽነት ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ የባለ ብዙ ባለድርሻ ምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።
በዚሁ ወቅት ሚኒስትሩ እንዳመለከቱት፤ በ2030 ዓ.ም የንፁህ መጠጥ ውሃ በገጠርና በከተማ ሙሉ በሙሉ ተደራሽ ለማድረግ ታቅዷል።
ይህንን ዕቅድ እውን ለማድረግም ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
የንፁህ ውሃ አቅርቦትን ማሳደግ ላይ ትኩረቱን አድርጎ እየመከረ ባለው በዚህ የባለ ብዙ ባለድርሻ መድረክ የፌደራልና ክልሎች መንግስታት፣ የልማት አጋሮች፣ የሲቪል ማህበራትና የሙያ ማህበራት ተገኝተዋል።
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።