በምክትል ርዕሰ መሥተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል ማኅበራዊ ክላስተር አስተባባሪ አብዱልሃኪም ሙሉ በአርሲ ዞን የተገነቡ ፕሮጀክቶችን እየመረቁ ነው፡፡
ፕሮጀክቶቹ በተያዘላቸው የጥራት ደረጃ እና ጊዜ ተገንብተው መመረቃቸውንም አቶ አብዱልሃኪም ገልጸዋል፡፡
ከተመረቁት ፕሮጀክቶች መካከል የኢተያ ገጠር ሽግግር ማዕከል አንዱ መሆኑን ጠቅሰው÷ ማዕከሉ በአካባቢው ያለውን የግብርና ግብዓት እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ እንደሚያግዝ አስገንዝበዋል፡፡
የኦሮሚያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ልማት ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ መንግሥቱ ረጋሳ በበኩላቸው በክልሉ ተመሳሳይ ሥድስት ማዕከላት መገንባታቸውን በመግለጽ÷ የማዕከላቱ መገንባት ለአርሶ አደሮችም ሆነ ለባለሃብቶች ከፍተኛ ጥቅም አለው ብለዋል፡፡
ሕብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ 1 ሺህ 61 ለተለያየ አገልግሎት የሚውሉ ፕሮጀክቶች በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት መሠራታቸውን የገለጹት ደግሞ አርሲ ዞን ዋና አሥተዳዳሪ ኢብራሂም ከድር ናቸው፡፡
በአጠቃላይ በዞኑ እየተመረቁ ለሚገኙ ፕሮጀክቶችም 5 ነጥብ 7 ቢሊየን ብር ወጪ መደረጉ ተመላክቷል፡፡
FBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።