July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ፖላንድ ሪፐብሊክ ርዕሰ መዲና ዋርሶ አዲስ በረራ ጀመረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዛሬው ዕለት ወደ ፖላንድ ሪፐብሊክ ርዕሰ መዲና ዋርሶ አዲስ በረራ ጀመሩን አስታውቋል።አዲሱ በረራ በሳምንት አራት ቀናት እንደሚደረግ የተገለጸ ሲሆን፤ በአፍሪካ እና በፖላንድ መካከል ያለውን ሁለንተናዊ ግንኙነት ወደ አዲስ ምዕራፍ የሚያሻግር እንደሚሆን ከአየር መንገዱ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ ትልቁ የአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ እንደሆነም ይነገርለታል።

EBC