የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ስዊስ ዲያግኖስቲክስ ኢትዮጵያን ጎብኝተዋል፡፡ የህክምና ማዕከሉ አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ለማድረግ የተጀመረውን ራዕይ ለማሳካት እንደሚያግዝ ከንቲባዋ ገልጸዋል፡፡ የማዕከሉ አገልግሎት እንዲስፋፋ እና ሌሎች የግል ባለሃብቶች በጤናው ዘርፍ ይበልጥ እንዲሰማሩ የከተማ አስተዳደሩ ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል፡፡ መሰል የጤና ማዕከላት መበራከት ከሃገር ወጥተው መታከም የማይችሉ ወገኖች የተሻለ ህክምና እንዲያገኙ ከማስቻሉም ባሻገር የውጪ ምንዛሬን እንደሚያስቀር ከንቲባዋ በማኀበራዊ የትስስር ገጻቸው ላይ አስፍረዋል፡፡
EBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ