July 2, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ፕሬዝዳንት ፑቲን የኑክሌር አረር የታጠቁ ሚኤሎች እንዲሰሩ አዘዙ

አሜሪካ እና ሩሲያ የመካከለኛ እና አጭር ርቀት የኑክሌር አረር ሚሳኤሎችን ላለማምረት ስምምነት ነበራቸው

አሜሪካ ይህንን ስምምነት በመጣስ በፊሊፒንስ እና ዴንማርክ ተመሳሳይ ሚሳኤሎችን አስፍራለች ተብሏል

ፕሬዝዳንት ፑቲን የኑክሌር አረር የታጠቁ ሚኤሎች እንዲሰሩ አዘዙ፡፡

ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት መጠናቀቅ በኋላ ዓለማችን ከባድ የጦር መሳሪያ ማምረት ፉክክክር ውስጥ ገብታ የነበረ ሲሆን ዋነኞቹ ተፎካካሪዎች ደግሞ አሜሪካ እና ሶቪየት ህብረት ነበሩ፡፡

የወቅቱ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሮናልድ ሬገን እና የሶቭየት ህብረት ፕሬዝዳንት ሚካኤል ጎርባቾቭ መካከለኛ እና የአጭር ርቀት የሚጓዙ ኑክሌር አረር የተገጠመላቸው ሚሳኤሎችን ላለማምረት ከ37 ዓመት በፊት ስምምነት ተፈራርመው ነበር፡፡

ይሁንና ዶናልድ ትራምፕ በፈረንጆቹ 2019 ላይ ሩሲያ ይህንን ስምምነት እያከበረች አይደለም፣ አሜሪካ በዚህ ስምምነት ታጥራ እያለ ቻይና በጎን እያመረተች እና አነው በሚል ስምምነቱን በይፋ ሰርዘዋል፡፡

Al-Ain