የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ከኬንያ መንገድ እና ትራንስፖርት ካቢኔ ፀሃፊ ኪፕቹምባ ሞርኮሜን ጋር በጋራ ጉዳዮች ዙሪያ በናይሮቢ ተወያይተዋል።በውይይታቸውም የሁለትዮሽ እና ቀጣናዊ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ዘርፍ ጉዳዮች ላይ የተወያዩ ሲሆን፤ በተለይም ሁለቱን ሀገራት በመሰረተ ልማት ማስተሳሰር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል።በተጨማሪም በኢትዮጵያ እና በኬንያ መካከል የጋራ የንግድ እና የኢኮኖሚ ዕድገት ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ማድረጋቸው ተገልጿል።በውይይቱ በኬንያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ጄነራል ባጫ ደበሌ መሳተፋቸውን ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
EBC
More Stories
የዩክሬን አየር ሃይል 106 የሩሲያ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትቶ መጣሉን አስታውቋል፡፡
ትራምፕ ጦርነቱን በመጀመር እና ስምምነት ላይ ባለመድረስ ዩክሬንን ወቀሱ
የማሻ ወረዳ ምክር ቤት 4 ኛ ዙር12ኛ ዓመት የሥራ ዘመን12 ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።