ከሶማሌላንድ ጋር የተደረገውን የመግባቢያ ስምምነት አስመልክቶ በዲጂታል ሚዲያው ላይ እየተሰራጩ ያሉ ሀሰተኛ መረጃዎችን ህብረተሰቡ እንዲጠነቀቅ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አሳስቧል፡፡ አካባቢያዊ፣ ክልላዊ እና ዓለምአቀፋዊ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ይፋዊ ግንኙነቶች በፅህፈት ቤቱ ይፋዊ የዲጂታል አማራጮች ብቻ እንደሚሰራጩ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የፅህፈት ቤቱን ሎጎ አላግባብ በመጠቀም የውሸት መረጃዎችን ከሚያሰራጩ አካላት ማህበረሰቡ እራሱን እንዲጠብቅም የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አሳስቧል፡፡
EBC
More Stories
የማሻ ከተማ አጠቃላይ ሆስፒታል ያለበትን የስራ ደረጃን በአንድራቻ ወረዳ አስተዳዳሪ በአቶ አየለ አገሎ የተመራ ቡድን መስክ ምልከታ አደርገዋል።
በሀሰተኛ ባለአንድ መቶ ብር ግብይት በመፈፀም ላይ የነበሩ ሁለት ተጠርጣሪዎችን ከያዙት ሀሰተኛ ገንዘብ ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የቦንጋ ከተማ ፖሊስ አስታወቀ
መከላከያ ሠራዊት ኢትዮጵያን ከመጠበቅ ባሻገር ለሀገሪቱ ስፖርት ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል – ሌተናል ጀነራል አለምሸት ደግፌ