በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ዛሬ ጅቡቲ የገባ ሲሆን ከጅቡቲ አቻቸው ማህሙድ አሊ የሱፍ ጋር ውይይት አድርገዋል። በውይይታቸውም፤ ሁለቱ ወገኖች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ማጠናከር እና ቁልፍ ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ መስራት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል። ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በኢኮኖሚ፣ በንግድ፣ የወደብ አገልግሎቶችን በተመለከተ ያላቸውን ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይም ምክክር መደረጉን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ አመላክቷል።
EBC
More Stories
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ
ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ኢትዮጵያና ዑጋንዳ በቀጣናው ሰላምና ፀጥታን በማስፈን ረገድ ጉልህ ሚና አላቸው አሉ
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በኮምቦልቻ ከተማ ተጀመረ