July 2, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ከ247 ሚሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተያዙ

247 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን የጉሙሩክ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡ዕቃዎቹ የተያዙትም ከሰኔ 7 እስከ 13 ቀን 2016 ዓ.ም በተደረገ ክትትል መሆኑ ተገልጿል፡፡በዚሁ መሠረትም 233 ነጥብ 8 ሚሊየን ብር የገቢ እና 14 ሚሊየን ብር የወጪ ኮንትሮባድ ዕቃዎች በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች መያዛቸውን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

FBC