የኢፌዴሪ መከላከያ ጀኔራል መኮንኖች አዲስ አበባ ከሚኖሩ የአማራ ክልል ተወላጆች ጋር በዛሬው ዕለት በዓድዋ ድል መታሰቢያ አዳራሽ ውይይት አካሂደዋል፡፡
የአማራ ክልል የሰላም ኮንፈረንሰ ውይይት ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተደርጓል፡፡
ወይይቱን የመሩት የክልሉ ተወላጅ የሆኑት የጦር ሃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጀኔራል አበባው ታደሰ ÷ የፌደራል ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነር ጀኔራል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ ዋና መምሪያ ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል በላይ ስዩም ናቸው።
ተሳታፊዎችም አለ የሚሉትን ችግር በነፃነት በጥያቄም በሃሳብም የገለፁ ሲሆን ÷ ጥያቄያቸው ለክልል መንግስት እና ለፌደራል መንግስት ተደራጅቶ እንደሚቀርብ ተገልጿል።
በጉባኤው ማጠቃለያው የመድረኩ ተሳታፊዎች ባለ 7 ነጥብ የአቋም መግለጫም አውጥተዋል መባሉን የመከላከያ ሠራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ