ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሰሜን ኢትዮጵያ በተከሰተው ግጭት ምክንያት ከጥቅምት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ተዘግቶ መቆየቱ ይታወቃል።ጽ/ቤቱ ሰኔ 11፣ 2016 ዓ.ም ዳግም አገልግሎት መስጠት የጀመረ ሲሆን፤ በጊዜያዊነት የጀመራቸው አገልግሎቶች ፓስፖርት ማደስ፣ የጠፋ ፓስፖርት መተካት እና የተበላሸ ፓስፖርት እርማት መስጠት ናቸው።በቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ፓስፖርታቸውን ሲያሳድሱ የነበሩ የመቐለ ከተማ ነዋሪዎች የቅርንጫፉ አገልግሎት በመቋረጡ ምክንያት አዲስ አበባ ድረስ ለመሄድ ይገደዱ እንደነበር ገልጸዋል።በዚህም ለአላስፈላጊ እንግልት ተዳርገው እንደነበር ጠቅሰው ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ዳግም ስራ በመጀመሩ መደሰታቸውን መግለጻቸውን ከኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
FBC
More Stories
“አስቸኳይ ፓስፖርት እናሰራላችኋለን” በሚል ሰዎችን ሲያጭበረብሩ ነበሩ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ተያዙ
3ኛው የፓርላማ ዜጎች ፎረም እየተካሄደ ነው
ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሚደረገው ድጋፍ እንዲጠናከር ጥሪ ቀረበ