የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ከተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ፕሬዚዳንት ዴኒስ ፍራንሲስ ጋር ተወያዩ።አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴና ፕሬዚዳንት ዴኒስ ፍራንሲስ በጋራ በሚሰሩባቸው ጉዳዮችና በአፍሪካ ቀንድ አገራት የሰላም ማስከበር ጉዳዮች ዙሪያ ላይ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብዩ ተድላ ተናግረዋል።የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አየር ንብረት ለውጥን ጨምሮ የታዳጊ አገራት አጀንዳዎች በሆኑ የፋይናንስ፣ የቴክኖሎጂ የአቅም ግንባታ ድጋፎች እንዲሁም በዘላቂ ልማት ግቦች ማረጋገጥ ጉዳዮችም እንደተወያዩ አንስተዋል።አምባሳደር ታዬ አፅቀሥላሴ ኢትዮጵያ ባለብዙ ወገን ዲፕሎማሲ የምትሰጠውን ትልቅ ቦታ እንዲሁም በቀጣይ በሚካሄደው ‘summit of future’ የተሰኘውን ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተመለከተም ዝርዝር ውይይት ስለማድረጋቸው ጠቅሰዋል።አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት ቋሚ መቀመጫ እንድታገኝ በሚደረግ ጥረትና መሰል የፀጥታ ጉዳዮችም የውይይቱ አካል መሆናቸውን ጠቅሰዋል።ይህ በእንዲህ እንዳለ ፕሬዚዳንቱ ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላምና መረጋጋት እንዲሰፍን የምታደርገውን ጥረት ማድነቃቸውን ቃል አቀባዩ አንስተዋል።መንግስት ውስጣዊ ግጭቶች በሰላም እንዲፈታ የያዘውን ቁርጠኛ አቋም ማድነቃቸውንም እንዲሁ ።ለልማት እንቅስቃሴዎችም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ ስለመሆኑም አንስተዋል።
Woreda to World
More Stories
ኢትዮጵያ የፊታችን ነሀሴ በአንካራ በሚካሄደው ድርድር ምን ትጠብቃለች?
የአይቻልም እና የአይሆንም መንፈስን መስበር ከተቻለ የማይቻል ነገር የለም “- ተማሪ ወጋየሁ ወራጆ
ዛሬ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ለምክር ቤቱ ማብራሪያ ይሰጣሉ