July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

በህንድ ሁለት ባቡሮች ተጋጭተው የ13 ሰዎች ህይወት አለፈ

ፖሊስ በህይወት የተረፉ ሰዎችን ለመታደግ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና የአደጋውን መንስኤ እያጣራ መሆኑን አስታውቋልበህንድ በደረሰ የባቡር ግጭት አደጋ እስካሁን የ13 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 30 ሰዎች ደግሞ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተነግሯል።አደጋው የደረሰው የመንገደኞች እና እቃ ጫኝ ባቡሮች በመጋጨታቸው እንደሆነ የገለጸው የአካባቢው ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ እያጣራሁ ነው ብሏል።በምስራቅ ህንድ ዌስት ቤንጋል ክልል የደረሰውን አደጋ ተከትሎ የነፍስ አድን ሰራተኞች በሕይወት የተረፉ ሰዎችን በማፈላለግ ላይ ይገኛሉ።