ከሳምንታት በፊት በ34 ክሶች ጥፋተኛ የተባሉት ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ቅስቀሳቸውን እንደቀጠሉ ናቸው
ዶናልድ ትራምፕ ምክትላቸው ጥቁር አሜሪካዊ አልያም ሴት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል
ዶናልድ ትራምፕ ስምንት እጩ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አጩ።
ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዩ ሕዳር ወር ላይ በሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ሪፐብሊካን ፓርቲን ወክለው እንደሚወዳደሩ ይጠበቃል።
አስገድዶ ደፈራ እና ግብር መሰወርን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው ዶናልድ ትራምፕ እጩ ምክትል ፕሬዝዳንት በቅርቡ እንደሚመርጡ አስታውቀዋል።
በአሜሪካ ፖለቲካ የመራጮችን ድምጽ ለማግኘት በሚል ከምርጫ በፊት የምክትል ፕሬዝዳንትን ማንነት ማሳወቅ የተለመደ ነው።
ዶናልድ ትራምፕም ለዚህ እንዲረዳቸው ስምንት እጩ ምክትል ፕሬዝዳንት ያሳወቁ ሲሆን የእጩዎች ገንዘብ ሁኔታ፣ ፈቃደኝነት እና ሌሎች መረጃዎች እየተሰባሰቡ እንደሆነ ተገልጿል።
Al-Ain
More Stories
ሩሲያ በዩክሬን የኢነርጂ መሰረተ ልማት ተቋማት ላይ የምትፈጽመውን ጥቃት ለማቆም ተስማማች
አሜሪካ በየመን የሀውቲ ታጣቂዎች ላይ አዲስ የአየር ጥቃት መፈጸሟ ተገለጸ
ትራምፕ “የወንበዴ” ቡድን አባላት ናቸው ያሏቸውን ከ200 በላይ ቬንዙዌላውያን ከአሜሪካ አባረሩ