July 4, 2024

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ዶናልድ ትራምፕ ስምንት እጩ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አጩ

ከሳምንታት በፊት በ34 ክሶች ጥፋተኛ የተባሉት ዶናልድ ትራምፕ የፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ቅስቀሳቸውን እንደቀጠሉ ናቸው

ዶናልድ ትራምፕ ምክትላቸው ጥቁር አሜሪካዊ አልያም ሴት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል

ዶናልድ ትራምፕ ስምንት እጩ ምክትል ፕሬዝዳንቶችን አጩ።

ዶናልድ ትራምፕ በቀጣዩ ሕዳር ወር ላይ በሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ላይ ሪፐብሊካን ፓርቲን ወክለው እንደሚወዳደሩ ይጠበቃል።

አስገድዶ ደፈራ እና ግብር መሰወርን ጨምሮ በተለያዩ ወንጀሎች ተጠርጥረው ክስ የተመሰረተባቸው ዶናልድ ትራምፕ እጩ ምክትል ፕሬዝዳንት በቅርቡ እንደሚመርጡ አስታውቀዋል።

በአሜሪካ ፖለቲካ የመራጮችን ድምጽ ለማግኘት በሚል ከምርጫ በፊት የምክትል ፕሬዝዳንትን ማንነት ማሳወቅ የተለመደ ነው።

 ዶናልድ ትራምፕም ለዚህ እንዲረዳቸው ስምንት እጩ ምክትል ፕሬዝዳንት ያሳወቁ ሲሆን የእጩዎች ገንዘብ ሁኔታ፣ ፈቃደኝነት እና ሌሎች መረጃዎች እየተሰባሰቡ እንደሆነ ተገልጿል።

Al-Ain